Pages

Sunday, November 27, 2011

አለማወቅህን

አለማወቅህን ደብቀህ ከምትኖር
እንዳልተረዳህው ሃቁን ብትናገር
ነገ ከሚመጣው አስጠያቂ ነገር
ወይ ልኩን ካለፈ ማትወጣው ችግር
እርስክን ማዳንህ መከለልህ ነበር
ብራናን ብራና ያስባለው እውነቱ
እራሱን መቀየር ነው እንጅ መልፋቱ
ቆዳ አልነበረም ወይ ሲፈጠር ከጥንቱ
ከብራና ተማር
እርሳን መቀየር
ግን እንደባር ማሽላ ውስጥህ አረማሞ
ላይህ ተቀባብቶ ደህና ሁኖ ቀልሞ
አውቅለሁ አውቅለሁ ስትል ስታናፋ
እራስክን ደብቀህ ከላይ ስትደነፋ
ቀን የመጣ እንደሆን ምላሽ ሚያስፈልገው
ያን ጊዜ የት ትሄድ ያንተስ ጉድ ብዙ ነው
ያላወቀ ጋነም መቸ ወረደና
ወይም አለማወቅ መች ሃጥያት ሆነና
እንዲህ ተሽቆጥቁጠህ ደጅ የምትጠና
አዋቂ ለመባል በገና ለገና
እርስክን ደብቀህ ከራስህ
ለመኖር ስታስብ ያነኝውን ቀብረህ
ቢንጨበጨብልህ
እንቢልታ ቢነፋ አንቱ ቢበዛብህ
ያልተደከመለት ያልጣርክለት እውቀት
እንዲያው እንደመና ከሰማይ ለማግኘት
ቢያወጡ ቢያወርዱ በከንቱ ቢያስቡት
ጉምን መሰብሰብ ባቅማዳ ለመክተት






ቢሰርቅ ምን አለበት።


ከራበው ሰው ቢሰርቅ ምኑ ነው ሚያስደንቅ
እንዲያው ካልተባለ ነገር እናዳምቅ
የሚሰጠው ካጣ ትንሽ ፍርፋሪ
ወዲያ ለቆሻሻ ከሚደፋው ቀሪ
እየበሰበሰ ለነገ ሲቀመጥ
ይሄኛው ተርቦ ምጽዋትን ሲጠብቅ
ተርፎ ከሚሻግት ሻግቶ ከሚደፋ
በጎን ከሚያስኬደን ሰርክ እየከረፋ
አንድ ዳቦ ምነው ህይወት ለማቆየት
ሰረቀ አስብሎ ዱላ ሚያስይዝበት
ሌባውስ ነበረ ተርፎት የሚደፋው
ላንዷ ሆዱ ሳስቶ ትርፍ እሚያጋብሰው
በልጓም ለጉሞ ለራሱ እንዲመቸው
ጥሬውን ከብስል ያ የሚያማርጠው
ሌባው ዳኛ ሆኖ
ምስክሩ ደግሞ ተገዝቶ በመኖ
ሁለቱ ተባብረው
በዛ በተራበው
አንድ ዳ ቦ ለራብ ማስታገሻ
በበላ ይሉታል ሌባ ነው ቆሻሻ
ይወረውሩታል ወደሰሩት ዋሻ
ስሙን አስከፍተው እሰከ መጨረሻ
ስትጥለው እያየህ አንተ ስታማርጥ
ከመፍረድህ በፊት እሱን ከመቀጥቀጥ
ቢበላ ምናለ ከትራፊው አንዷን
የምትጨረውን ለማስታገስ ሆዱን