Pages

Sunday, November 27, 2011

አለማወቅህን

አለማወቅህን ደብቀህ ከምትኖር
እንዳልተረዳህው ሃቁን ብትናገር
ነገ ከሚመጣው አስጠያቂ ነገር
ወይ ልኩን ካለፈ ማትወጣው ችግር
እርስክን ማዳንህ መከለልህ ነበር
ብራናን ብራና ያስባለው እውነቱ
እራሱን መቀየር ነው እንጅ መልፋቱ
ቆዳ አልነበረም ወይ ሲፈጠር ከጥንቱ
ከብራና ተማር
እርሳን መቀየር
ግን እንደባር ማሽላ ውስጥህ አረማሞ
ላይህ ተቀባብቶ ደህና ሁኖ ቀልሞ
አውቅለሁ አውቅለሁ ስትል ስታናፋ
እራስክን ደብቀህ ከላይ ስትደነፋ
ቀን የመጣ እንደሆን ምላሽ ሚያስፈልገው
ያን ጊዜ የት ትሄድ ያንተስ ጉድ ብዙ ነው
ያላወቀ ጋነም መቸ ወረደና
ወይም አለማወቅ መች ሃጥያት ሆነና
እንዲህ ተሽቆጥቁጠህ ደጅ የምትጠና
አዋቂ ለመባል በገና ለገና
እርስክን ደብቀህ ከራስህ
ለመኖር ስታስብ ያነኝውን ቀብረህ
ቢንጨበጨብልህ
እንቢልታ ቢነፋ አንቱ ቢበዛብህ
ያልተደከመለት ያልጣርክለት እውቀት
እንዲያው እንደመና ከሰማይ ለማግኘት
ቢያወጡ ቢያወርዱ በከንቱ ቢያስቡት
ጉምን መሰብሰብ ባቅማዳ ለመክተት






No comments:

Post a Comment